በኢትዮጵያ ምድር፥ ምኒልክን (ዮሴፍን) ‘ማያውቅ፥ አዲስ ንጉሥ መ’ቶ፣ “ለነፃነት” ብሎ፥ የነፃነትን ጧፍ፥ ረጋግጦ አጥፍቶ፣ “ከኔ ወዲያ ላሳር!”፥ አለን አፉን ሞልቶ፣ ያ’ባቶችን ክብር፥ አፈር መሬት ከ’ቶ። ያገሬ ፈርዖን፥ ልቡ እጅግ ደንድኖ፣ የፈጣሪን ፈቃድ፥ እንዳይሰማ ሆኖ፣ “እንደ’ኔ ያለ ንጉሥ!”፥ እያለ ይጽናናል፣ የበትሩን ምሬት፥ በጠገበ ጉልበት፥ ከተማን ያጸናል። ስንት አሮን ተላከ? ስንት ሙሴ መጣ? “የሠራዊት ጌታ፥ ‘ህዝቤን ልቀቅ’ [...]
↧