Quantcast
Channel: Goolgule
Viewing all 3173 articles
Browse latest View live

በጭቃ ላይ ጭቃ…

$
0
0
….”ታጥቦ ጭቃ” እንዳንል ከመነሻው ከአንጀቱ ሊታጠብ የሞከረም የለ… ይሄ መከረኛ ህዝብ ግን ስንቱን ቁስል ጠባሳ አድርጎ ሊኖር ይቻለዋል? እንዴትስ፣ እስከመቼስ እንዲህ ይዘለቃል? ያላከምነው ቁስል ሲያመረቅዝ እያየነው ሌላ ቁስል መፍጠርንስ ምን ይሉታል? እንዲህ ያለውን ነገር ምን ብለው፣ ምን ሰበብ ፈጥረው፣ ምን ወሬ አባዝተው፣ እንዴትስ አሸሞንሙነው አደባበሰው ያልፉታል? ተዉ…ተዉ…. ወደፊት መሄድ እንጂ ወደ ነበሩበት መመለስ መንገድን አያሳጥርም። […]

“ጃ ያስተሰርያል!”አራት አመታት ተከልክሎ በነበረ መድረክ?

$
0
0
ቴዲ ወደ ባህርዳር ሲያቀና “እንዘምራለን” ማለቱን ያስተውሏል! የጉዞውን አላማ እንዲያ ሲል ነበር ረቂቅ በሆነ መንገድ የገልጸው። በመዘመር እና በመዝፈን መሃል ያለውን ጥልቅ ልዩነት የማይረዳ ብቻ ነው ለሰሞኑ “አሲዮ ቤሌማ” እጅ የሚሰጠው። ከኮንሰርቱ ጀርባ ያለው “የፍቅር ጉዞ” የሚለው መሪ ቃል ውስጥም ከውቅያኖስ የጠለቀ መልዕክት አለ። ይህንን ቃል የተረዳ ብቻ ነው የተልእኮውን ስኬት ሊያበስር የሚችለው። ዝግጅቱ ኮንሰርት […]

ሕዝብ ፍርሃትን እያሸነፈ፤ የወያኔም ጀንበር እየጠለቀች ነው!

$
0
0
ፍርሃትን እያሰረጸና እያነገሰ የኖረው ፖለቲካችን ነጻነታችንን፣ ክብራችንን፣ ታሪካችንን፣ ስብዕናችን እና አብሮነታችንንም ጭምር ሲያኮስስና ሲያረክስ፤ እንዲሁም የወደፊት ተስፋችንም ላይ ጥላውን ሲያጠላ እያየን ነው።  የማንኛውም አንባገነናዊ ሥርዓት ሥነ-ልቦናዊ መሰረቱ ፍርሃት ነው። አንባገነኖች ያላቸውን ኃይል ሁሉ የሚያሟጥጡት ሕዝብን በማሸበር የፍርሃት ቆፈን ውስጥ እንዲቆይ በማድረግ ነው። ለዚህም አራት ነገሮችን በዋነኝነት ይጠቀማሉ። የመጀመሪያው የጡንቻቸውን ልክ ለማሳየት ዱላና ጠመንጃን በመጠቀም የጭካኔ […]

TIBIBIR Press Release on the tragic events in Weldya

$
0
0
TIBIBIR, a Consortium of more than 20 Ethiopian Civic groups, based throughout the world is deeply disturbed by the recent events in Weldia, a town located in northern Ethiopia. Credible reports from the area as well as a report from the United Nations have stated that on January 20, 2018, Ethiopian security forces have shot […]

The Ethiopian Diaspora Flexing its Muscle Against a Killer Regime in Addis Ababa

$
0
0
(Our hard-earned foreign currency should help our beloved families, not TPLF Killers and Torturers) Ethiopian diaspora residing in industrialized nations have their country and their family at heart, so they sacrifice a lot to helping immediate and extended families in their homeland.  It is very common among Ethiopians, as it is for most immigrants from […]

ፍትሕ ለዐማራ ሕዝብ!

$
0
0
ኢትዮጵያ አገራችን በዘመኗ ሁሉ ብዙ ፈተናዎችን አሳልፋለች።አሁን የገጠማት በዓይነቱም ሆነ በብዛቱ በወርዱም ሆነ በቁመቱ ዘመናት ከደቀኑባት ሁሉ የተለየ ነው።ከዚህ ውስጥ አንዱ ሕዝቦቿ ጎራ ለይተው በጎጥ ተቧድነው፣ ዘረኞች እር በርሳቸው እንዲፋጁ የደገሱላት የመጠፋፋት ድግሥ ነው። ለዚህ ዕኩይ ግባቸው የመስዋዕት ጠቦት ያደረጉት ደግሞ ዐማራውን ነው። ወደ ተሻለና የሁሉም ዕኩልነት የተረጋገጠባት ዴሞክራሲያዊት አገር እንደመመሥረት እና ሁኔታዎችም ይህንኑ ፈቅደውላቸው […]

የገዱ አንዳርጋቸው መግለጫ ሲተረጎም

$
0
0
ኦቦ ለማ መገርሳ ህወሃት ያጎራቸውን 2,345 እስረኞች ነጻ አወጡ የሚለውን ዜና በቀኝ እየሰማን፣ የገዱ አንዳርጋቸው መግለጫ ደግሞ በግራ በኩል ብቅ አለ። ሰበር ጋዜጣዊ መግለጫ። በርግጥም “ወገብ የሚሰብር”። ልዩ መግለጫው ተከባብዶ ሲነገረን “ገዱ ደግሞ ስንት ሺህ አማሮችን ከእስር አስለቀቀ” እያልን በጉጉት ባንጠብቅም “የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ሕዝቦች ሆይ በወልድያ እና በቆቦ ለተፈጸመው እልቂት ተጠያቂው እኔ የምመራው ብአዴን […]

“የሃይማኖት አባቶች” የሰላም ጥሪ

$
0
0
“ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት ስንት ወልድያ ያስፈልገናል?” ዳንኤል ክብረት በትናንት ምሽቱ የ“ሰላም ዋጋ” ዲስኩር አፈሙዝ ሳይሆን “ዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን” ተወግዟል። የሃገሪቱ እድገት እና ትራንስፎርሜሽንም ተወድሷል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ዻዻስ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቴያስ ፓትሪያሪክ፣ ርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳት ዘአክሱም ወጨጌ፣  ዘመንበረ ተክለሐይማኖት….  ወዘተ  “… (ሃገሪቱ) ለሁሉም ልጆችዋ የምታበላው ከሌላት ከየት ታምጣ?” ብለውናል። “ሕዝቡ ቢያገኝም […]

WHAT KIND OF LEADERSHIP IS NEEDED IN ETHIOPIA TO AVERT ETHNIC VIOLENCE AT THIS TIME OF CRISIS?

$
0
0
Is the TPLF willing to take the country down with them, thinking they could simply secede from the country as an escape plan and leave the rest with chaos? Allegedly, the TPLF and some of the people of Tigray are seriously considering seceding from Ethiopia, believing they can no longer safely “lead” the country due […]

የወሎ ዐማራ የሰሞኑ ጉዳይ ማጠቃለያ ሪፖርት (የእስካሁኑ ሒደት)

$
0
0
የትግሬ ወያኔ አፈ ቀላጤዎች ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃት በወልዲያና በመርሣ ቆቦ አካባቢ እንደደረሰ ኡኡታቸውን ሲያሰሙ ሰንብተዋል። ዕውነታው ግን ሌላ ነው። የወሎ ዐማራ ጠላቱን በደንብ ለይቶ ነው ጥቃት ያደረሰው። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ከትግሬዎች ንብረት በላይ የዐማራ ተወላጅ (ባንዶች) ንብረት ላይ ነው ጉዳት የደረሰው። ሁሉንም በዝርዝር ከዚህ በታች አቅርበነዋል። በባንዳ ዐማሮች ላይ የተወሰደው እርምጃ አስተማሪ ይመስለኛል። ሰውን […]

Ailing Civic Space in an Authoritarian State: The State of Human Rights Defenders and Cost of Dissent in Ethiopia

$
0
0
Journalists, activists, and other civil society actors play a pivotal role in building a transparent system of governance in any society. The UN Declaration on Human Rights Defenders* affirms that everyone, individually and in association with others, has the right to submit to governmental public bodies, criticism and proposals for improving their functioning, and to […]

“እናንተ ሰው ናችሁ?”ትራምፕ ለአፍሪካ መሪዎች

$
0
0
ከዚህ በታች የተጻፈውን ፕሬዚደንት ትራምፕ አለ ተብሎ  ፌስቡክ ላይ ያገኘሁት ነው፤ “ነፃነታችሁን ካገኛችሁ ከ50 ዓመታችሁ በኋላ ለሕዝቦቻችሁ አስፈላጊውን የመገናኛ ዘዴ ካልሠራችሁላቸው እናንተ ሰው ናችሁ? እናንተ በወርቅ ላይ፣ በዕንቁ ላይ፣ በዘይት ላይ፣ በማንጋኒዝ ላይ፣ በዩራኒየም ላይ ተቀምጣችሁ ሕዝቦቻችሁ የሚበሉት ሳይኖራቸው ሲቀር እናንተ ሰው ናችሁ? እናንተ በሥልጣን ላይ ሆናችሁ የጦር መሣሪያ ከባዕዳን ለመግዛትና ዜጎቻችሁን ለመግደል የማታመነቱ ከሆነ እናንተ ሰው […]

መሆን ካልነበረበት ድርጊት ጋር ስንላመድ

$
0
0
(ለውይይት መነሻ) በዚህ ጽሁፌ ላንባቢዎቼ ለማቅረብ የፈለግሁት ሁለት ተያያዥ ጉዳዮችን ነው። የመጀመርያው፣ ወያኔ ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ሲፈጽማቸው የነበረውን “ነውሮች” እንዴት እንደ “ጽድቅ” እንደተጠቀማባቸውና የኢትዮጵያንም ህዝብ “ጽድቅ” ነው ብላችሁ ተቀበሉ ብሎ እንዳስገደንና እኛም በመላመድ ብዛት ተዋህዶን እንደተቀበልነው፣ ሁለተኛው ደግሞ ይህንን “ነውር” እንደ “ጽድቅ” በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ጭኖ ሲበድል የነበረው ወያኔ (ህወሃት)፣ በምንም መልኩ የትግራይን ህዝብ […]

ህወሓትና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዓላማው!

$
0
0
የአዘጋጆቹ ማስታወሻ፤ ባለፉት ዓመታት ከህወሓት እየኮበለሉ የወጡ የቀድሞ አባላት በርካታ ናቸው። እንዳንዳቸው የሚወጡበት ምክንያት ቢኖራቸውም ህወሃትን በማጋለጥና ማንነቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በማሳወቅ የአቶ ገብረመድኅን አርአያን ያህል ታላቅ ሥራ የሠራና መስዋዕትነት የከፈለ አለ ለማለት ያስቸግራል። አብዛኛዎቹ የቀድሞው አባላቱ የህወሓትን ምሥጢራዊ አሠራር እና እጅግ አረመኔያዊ ግፍ፤ ኤፈርት በኢትዮጵያ ሐብት ላይ የፈጸመውንና እስካሁንም እየፈጸመ ያለውን የኢኮኖሚ ግፍ፣ ዝርፊያ፣ ሌብነት፣ […]

ሕዝባዊ ጽናትና የHR 128 ጡንቻ “እስረኞች”ን አስፈቱ

$
0
0
አገሪቱን ከሁሉም አቅጣጫዎች ለዓመታት ሲያናውጥ የቆየው ሕዝባዊ ዓመጽ ከHR 128 ጋር ተዳምሮበት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገባው ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እያለ በግፍ ያሰራቸውን እየፈታ ነው። የተፈቱት ተመልሰው ላለመታሰራቸው ምንም ዋስትና የለም ተብሏል። ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዚዳንትነቱን መንበር ከተረከቡ ጊዜ ጀምሮ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) የተባለው አሸባሪ የበረሃ ወንበዴዎች ቡድን ስሉሱ እንደዞረበት አስተውሎ የራሱን ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል። […]

በኢትዮጵያ የመፈንቅለ መንግሥት ይዘት ያለው ወታደራዊ አገዛዝ ሊታወጅ ነው!

$
0
0
በኢትዮጵያ በተከታታይ የዘለቀውን ሕዝባዊ ተቃውሞ መቆጣጠር የተሳነው ህወሓት በኢትዮጵያ በአስቸኳይ አዋጅ ስም አገሪቷን በወታደራዊ አስተዳደር ስር ለማስተዳደር ኣዋጅ አንደሚያወጣ ተሰማ። የመፈንቅለ መንግሥት ይዘት ያለው አዋጅ ምናልባትም ዛሬ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል። ያለፈው የኢህአዴግ ስብሰባ ወቅት ስምምነት ተደርሶበት የነበረው ሁሉንም ያሳተፈ የሽግግር መንግስት ምስረታ ህወሓት ኣልቀበለውም ብሏል፥ ይህንን ተከትሎ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከስልጣኑ እንዲወርድ በህወሓት ግፊት ሲደረግበት ቆይቷል፤ […]

ዘብረቅራቃው የባህር ዳር “ቅጠል ሰፈር”ጉድ!

$
0
0
ልብ-ወለድ ታሪኮችን አብዝቶ መጻፍ፣ ዕውነታዉን በግማሹም ቢሆን አስቶ፣ በራስህ የህልም ዓለም ዉስጥ እንድትዋኝ ያደርግሃል፡፡ የCreative writing ኪኑ ከአምላክ ቢሰጥህም፣ ጭቆናንና መገፋትን-ድህነትንና መቆራመድን በጠራ-ገለጥለጥ ባለ አማርኛ ከመግለጽ ግን አትታጎልም፡፡ የኔ ሁለት የሃሳብ ጽንፎች እንደዚህ ሲጓተቱ ቆይተው፣ በስተመጨረሻ “ዕውነታን በኪነት” አሉና ተስማሙ፡፡ ሰፈሬ ከከተማዋ (ከባህር ዳር) አንዷ ክፍል ሆና በመጠራት ትታወቃለች፡፡ በአሁኑ የቀበሌ አወቃቀር፣ “ክፍለ-ከተማ” ተባለች፤ “ሽምብጥ […]

ኃይለማርያም ደሳለኝ ለምን ለቀቁ?

$
0
0
ኢ.ቢ.ሲ. በሰበር ያስተናግደውን የኃይለማርያም ደሳለኝ መግለጫ፤ ዞምቢዎቹ ተሯሩጠው ለማጽደቅ ግዜ አልወሰደባቸውም። እሳቸውም ልክ ስልጣን እንደነበረው ጠቅላይ ሚኒስትር “ስልጣን አስረክቢያለሁ” ሲሉ እፍረት የሚባል ነገር ፊታቸው ላይ አይታይባቸውም ነበር። ሹመት እንጂ ሕገ-መንግስቱ የሚፈቅደው ስልጣን እጃቸው ላይ እንዳልነበር ሕጻናትም ያውቁታል። የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መልቀቅያቸውን በብርሃን ፍጥነት ሲያጸድቀው፤ ድርጊትዋን ከደቡብ አፍሪካው ጃኮብ ዙማ ክስተት ጋር ለማመሳሰል የተተወነች ድራማም […]

ለጠቅላይ ሚኒስትርነት የትኛው ኦህዴድ?

$
0
0
በደም ወይስ በድርጅት አባልነት? ወርቅነህ ገበየሁ ወዴት ወዴት? ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን ፍላጎት መኖሩን፣ እሱም ቦታውን እንደሚፈልገው የጎልጉል የመረጃ አቀባዮች ጠቆሙ። ወርቅነህ ቀደም ሲል ከነበረው ሃላፊነት፣ ኦሮሞ አይደለም በሚል የሚቀርብበት ክስ፣ በ1997 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለተካሄደው ግድያ ግንባር ቀደም ተጠያቂ ነው በሚል ስለሚወነጀል ኢህአዴግ ራሱ የበጠሰውን የሕዝብ እምነት ሊቀጥል አይችልም የሚል […]

የከረረው የአሜሪካና የህወሓት “ወዳጅነት ተበጥሷል”

$
0
0
አጋራችን ብትሆኑ ኤምባሲችን ወደየሩሳሌም እንዲዛወር ድምፅ ትሰጡ ነበር – አሜሪካ ለህወሓት ህወሓት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዳያውጅ በጌቶቹ ከተነገረው በኋላ በራሱ መንገድ መሄዱ የግንኙነት “ገመዱን እንደበጠሰው” ተነገረ። አሜሪካ ኤምባሲዋ ወደየሩሳሌም እንዳይሄድ የተቃወሙ አገራትን ዋጋ ትከፍላላችሁ ያለችውን በህወሓት ላይ ተግብራዋለች። አውሮጳውያን የጠነከረ ተቃውሟቸውን በህወሓት ላይ በዚህ ሳምንት ውስጥ እንደሚያሰሙ ይጠበቃል። በባራክ ኦባማ አስተዳደር የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት […]
Viewing all 3173 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>