Quantcast
Channel: Goolgule
Browsing all 3165 articles
Browse latest View live

በአስመጪ ዳዊት የማነ ሀሰተኛ ሰነድ ወደ ሀገር ዉስጥ ሊገባ የነበረ ገጀራ ተያዘ

ከፌደራል ፖሊስ ፈቃድ እንደተሰጠው በማስመሰል በተጭበረበረ ሰነድ ርክክብ ተፈጽሞ ባለቤት የተባለው ሰው ከተረከበ በኋላ በተደረገ ክትትል 186 ሺህ 240 ገጀራ በቁጥጥር ስር ዋለ። በጅምላ ጭፍጨፋ በተካሄደባቸው አገራት በተገኘ ልምድ ገጀራ ክልከላ የጣለበት የእጅ የጥፋት መሳሪያ ነው። ገጀራው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ...

View Article


ምዕራባውያን –“ለድርድር እናስገድዳለን ካልሆነ ወደ ዶ/ር ዐቢይ እንዞራለን”

ይህ ድምፅ የምዕራባውያኑ የመጨረሻው ድምፅ ነው። ወስነዋል። የመጨረሻውን ጫና ጀምረዋል። ጫናው እየጨመረ ይሄዳል። ለምን በአዲስ መልክ ጫናውን ጀመሩ ብንል ተስፋ አድርገውት የነበረው የተመድ የፀጥታው ም/ቤት እነሱ እንደሚፈልጉት ባለመወሰኑ ይመስላል። በክፍል 3 የመጨረሻ ካርዶችን እንይ:- 1ኛ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ...

View Article


ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና

ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ...

View Article

“በተለምዶ ‘ሸኔ’የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”

በርካቶች ‘ሸኔ’ እያለ እራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት እንዴት አሸባሪ ተብሎ ይሰየማል ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ስያሜ አንዳች ነገር ለመሸፈን ተፈልጎ ነው በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚገልፁ ምሁራንም አልጠፉም። ለመሆኑ ‘ሸኔ’ ማነው? በዚህ ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት የተጠየቁት የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌድዮን...

View Article

ዓለምአቀፉ አሸባሪ ትክክለኛ ስሙን አገኘ

ድልድይ በማፍረስ፤ መሠረተ ልማቶችን በማውደም ከየቦታው በተለቃቀሙ ወንበዴዎች መሪነት ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም በግፍ ሲገዛ የነበረው ህወሃት/ትህነግ ዛሬ ትክክለኛ ስሙን አገኘ። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት...

View Article


በአዲስ አበባ በ9 ወራት ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የመንገድ ጉዳት ደርሷል

በመዲናይቱ በ9 ወራት ብቻ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የመንገድ ኃብት ላይ ጉዳት ደርሷል። በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 179 የመንገድ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ይህም በገንዘብ ሲሰላ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ልዩ ልዩ የመንገድ ኃብት ላይ በተሽከርካሪ ግጭት ምክንያት...

View Article

በበጀት ዓመቱ 272 ማንሆል ክዳኖች ተሰርቀዋል –የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን በበጀት ዓመቱ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 272 ማንሆል ክዳን እንደተሰረቀበት አስታውቋል። ባለስልጣኑ በአሁኑ ሰዓት ከ1500 ኪሎ ሜትር በላይ የፍሳሽ መስመሮች በመዲናዋ ተዘርግተዋል ያለ ሲሆን የፍሳሽ መስመሮቹን የፍሰት መቆጣጠሪያነት እና ጽዳት ለመከታተል የሚያስችል...

View Article

ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ

በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በአንድ ግለሠብ መጋዘን ውስጥ  ተከዝኖ ተገኘ። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር  ቀበሌ ዐ5 ልዩ ቦታው ኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ በሚገኝ ለሙጫና እጣን ማቀነባበሪያ መጋዘን ውስጥ ከ6ሺ ኩንታል በቆሎ በላይ ተከዝኖ መገኘቱን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ...

View Article


“የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም” ፕ/ር በየነ

የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች መምጣት አለመምጣት በአገራዊው የምርጫ ሂደት ላይ የሚያሳድረው አንዳችም ተጽዕኖ እንደሌለ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)ፕሬዚዳንትና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አስታወቁ ። ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን...

View Article


በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ

በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በተደረገ ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 1 መቶ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ...

View Article

የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ

በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም አቅደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡ የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ በአዲስ አበባና በአንዳንድ...

View Article

ምርጫ ቦርድ የስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ ውጤት አሳወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በ440 የምርጫ ክልሎች የተከናወነውን አጠቃላይ ምርጫ  ውጤት ሐምሌ 3 ቀን 2013 ዓም  በስካይላይት ሆቴል በተከናወነ መርሐ ግብር ይፋ አደረገ፡፡ ቦርዱ እስካሁን በሒደት ካሳወቃቸው የተረጋገጡና ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶች በማስከተል ምርጫው በተከናወነ በ20...

View Article

“አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች

በተከታታይ በቲውተር ገጹ መረጃ የሚያሰራጨው የአሸባሪው ትህነግ አባል ጌታቸው ረዳ ትግራይን እንደማይመራ ክርክር ተነስቷል። የራያ ልጅ የሆነውና ፍጹም የአማራ ደም ያለው ባንዳው ጌታቸው ቀደም ሲል በዩኒቨርስቲ መምህርነቱ ወቅት በረኸኞቹን ትህነጎች “ህግ የማያውቁ፣ ደደቦች፤ ምንም የማይገባቸው፤ መሃይም ደናቁርት” እያለ...

View Article


ዳግማዊ ዓድዋ –የዓባይ ግድብ በጸጥታው ምክርቤት

የታላቁ የኢትዮጵያ ዓባይ ግድብ ውዝግብ ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ የነበረውን የአፍሪካ ኅብረት ሚና አጣጥለው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የፀጥታው ምክር ቤት መፍትሔ ለመሻት የሄዱት የታችኞቹ የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ግብፅና ሱዳን፣ የጠበቁትን ሳያገኙ በዓለም አደባባይ ሚናውን ወዳረከሱት የአፍሪካ ኅብረት...

View Article

ኮሜርሻል ኖሚኒስ የሕወሓት ባለሥልጣናት ሕንፃዎችን ሊያስተዳድር መሆኑ ተነገረ

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው ሕወሓት ቡድን አባላት ሕንፃዎችን በገለልተኛ አካል እንዲተዳደር በወሰነው መሠረት፣ ሕንፃዎቹን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ተረክቦ ሊያስተዳድር መሆኑ ተሰማ፡፡ በሰኔ 2013 ዓ.ም. አጋማሽ የሕወሓት ቡድን አባላት ንብረት የነበሩ ከ30 በላይ የንግድና የመኖሪያ ሕንፃዎች፣...

View Article


አዲስ አበባ ሳያርፉ በቀጥታ ወደ ትግራይ ክልል በአየር ዕርዳታ ማድረስ አይቻልም

ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ማስጠንቀቂያ መስጠቱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ።   መንግሥት ዓርብ ሐምሌ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳሰታወቀው፣ የተባበሩት መንግሥትታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ የሆነው ተቋም፣ የኢትዮጵያን...

View Article

አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት ተመራጮች

አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች አሏት፡፡ ሰኔ 14፤ 2013 በተካሔደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ፤ ከ23 የፓርላማ መቀመጫዎች ገዢው ብልጽግና ፓርቲ  በ22 የምርጫ ክልሎች ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ቅዳሜ ምሽት አስታውቋል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ  ያላቀረበበት ብቸኛ...

View Article


የመንግሥት ሚዲያዎች ፍትሃዊነታችንን አጉድላችሁብናል –ወ/ት ብርቱካን

“ዛሬ እዚህ የምትቀርጹን የመንግስት ሚዲያዎች በጣም በትህትና ልነግራችሁ እፈልጋለሁኝ። የመንግስት ባለሥልጣናት ኮታቸው ላይ የተሰካው ማይክራፎን የማይወልቅ ይመስል ሌት ተቀን የእነሱን ካምፔን እና ቅስቀሳ ስታስተላልፉ ቆይታችሁ የተቃዋሚዎችን 10 እና 15 ደቂቃ ማድረጋችሁ ፍትሃዊነታችንን አጉድሎብናል። እንዳላየ...

View Article

አርከበ ዑቅባይ ለUNIDO ዋና ዳይሬክተርነት ሳይመረጥ ቀረ

ጀርመናዊው ገርድ ሙለር ቀጣዩ የUNIDO ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተመርጠዋል አርከበ ዑቅባይ ለተባበሩት መንግስታት ኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት/UNIDO/ ዋና ዳይሬክተነት ሳይመረጥ ቀረ። በኢንዱስትሪ ልማት ስራዎች ላይ የካበተ ልምድ እንዳላቸው የሚታመንባቸው፣ የጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ ልዩ የኢኮኖሚ አማካሪ በመሆንና...

View Article

በአፍራሽ ሥራ የተጠመዱ የረድኤት ድርጅቶች ሊባረሩ ይችላሉ

የዕርዳታ አቅራቢዎች ከኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በአፍራሽ ስራ ላይ ተሰማርተዋል ያለቻቸውን አንዳንድ የእርዳታ አቅራቢዎችን ከሀገር ልታባርር እንደምትችል አስጠነቀቀች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥረው ነበር። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፥ “አንዳንድ የሰብዓዊ እርዳታ...

View Article
Browsing all 3165 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>