የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እሁድ ዕለት ያቀደውን ሰላማዊ ሠልፍ በ37 መፈክሮች በማጀብ አካሂዶዋል፡፡ አብዛኛዎቹ መፈክሮች ምርጫን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታን፣ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች መቆራረጥና መንግሥትን ከሃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲወጣ የሚጠይቁ ነበር፡፡ ከመፈክሮቹ መካከልም “ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንጂ በአስመሳይ ፕሮፖጋንዳ፣ በኃይልና በተፅዕኖ አይገነባም”፣ “የአገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሐዊ [...]
↧