እንግዲህ ያረጀ የአመፅ ታሪክ ከመድገም፤ ከውጭ አገር መፍትሔ ከመኮረጅና፤ እልከኛና አንገተ ደንዳና ሆነን ለአዲሱ ጤናማ ኢትዮጵያዊነት አስተሳሰብ የማንመች ከመሆን ይጠብቀን። በአይነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነውንና የኛው በኛው ለኛው ሆኖ የሚያኮራንን አዲስ የእርቅና የመግባባት ስሌትን መፍጠር እንችላለን የሚል አስተሳሰብ ይኑረን። እንቆቅልሻችንን እንፍታና የአገር ልጅነት ግዴታችንን በታማኝነት እንወጣ። በተቃራኒ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተከፋፈልን ህዝብ ብንሆንም፦ ጥላቻና ንቀትን አስወግደን፤ ሁለቱም ጎራ [...]
↧