የዓለም የጋዜጦችና ዜና አታሚዎች ማኅበር (WAN-IFRA) የ2014 የነጻነት ወርቅ ብዕር ሽልማቱን ለኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛና አሳታሚ እስክንድር ነጋ እንዲሰጥ መወሰኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቆዋል:: ህወሃት/ኢህአዴግ “የጸረ ሽብር ሕግ” በማለት ባወጣው አዋጅ ሰበብ እስክንድር ነጋ 18 ዓመት እንዲታሰር የተበየነበት መሆኑን መግለጫው ጨምሮ ገልጾዋል:: መግለጫው እስክንድርን ጨምሮ ሰሎሞን ከበደ፣ ውብሸት ታዬ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ዩሱፍ ጌታቸው ከእስር እንዲፈቱ አሳስቦዋል:: ኢትዮጵያን [...]
↧