የአንድነት ፓርቲ አመራር አካላት በፈረንጅ አቆጣጠር ኦገስት 30 ቀን ከሚድያ አካላት ጋር ያደረጉትን የቴሌ ኮንፈረንስ ውይይት በጥሞና ተከታትያለሁ:: መልካም ጅምር ቢሆንም ተደጋጋሚ ስህተቶች ከመፈጸም ግን የተቆጠብን አይመስልም:: በውይይቱ ላይ ብዙ መልካም ነገሮች ቢሰሙም የሚፈጸሙት ስህተቶች ግን ያው የጥንት የጠዋቱ በመሆኑ ውይይቱ ምን ያህል ወደፊት የሚያራምድ መሆኑ መገመት ይከብዳል:: የተንሸራሸሩት ሀሳቦች አዲስ ፈጽሞ የማናውቃቸው አይደሉም:: የተቃዋሚ [...]
↧